የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)

የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ከኢፌድሪ ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዋና መ/ቤትና ተጠሪ ተቋማት በጋራ “ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ቃል 22ኛው የአለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ተከብሯል፡፡
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) “ትውልድ በስነ-ምግባር ተኮትኩቶና ታንጾ ሲያድግ ተቋማት ከሙስና የጸዱና ተገቢውን አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ይሆናሉ” ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ከኢፌድሪ ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዋና መ/ቤትና ተጠሪ ተቋማት በጋራ “ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ቃል 22ኛው የአለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ተከብሯል፡፡
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) “ትውልድ በስነ-ምግባር ተኮትኩቶና ታንጾ ሲያድግ ተቋማት ከሙስና የጸዱና ተገቢውን አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ይሆናሉ” ብለዋል፡፡
ሙስና ከአስተሳሰብ እንደሚጀምር በመረዳት ከሙስና የጸዳች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አበይት የፀረ-ሙስና መርሆዎችን በተሟላ መልኩ መፈፀም እንደሚገባ አጽንኦት ሰጠተው ተናግረዋል።
አክለውም የፀረ-ሙስና ትግሉን ለማጠናከር ግልጸኝነት ያለው የአሠራር ስርዓትን መዘርጋት እና ቴክኖሎጂን በአግባቡ በመጠቀም አሰራሮችን ፈጣንና ተደራሽ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።
ሁሉም አመራሮችና ሰራተኞች ስነ-ምግባር የተላበሰና ከሌብነት የጸዳ ተቋም ለመፍጠር በትብብርና በቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አቅጣጫ ተቀምጧል።
በዚሁ መድረክ ላይ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር የሃብት ምዝገባ ሰነድ ርክክብ አድርገዋል።
በመጨረሻም ባለ 5 የአቋም መግለጫ በማስተላለፍ በዓሉ የተከበረ ሲሆን መላው ሰራተኛ ደግሞ በonline ሃብቱን በአጭር ጊዜ እንደሚያስመዘግብ ይጠበቃል፡፡