የኢተምድ አመራርና ሠራተኞች በ2018 ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡
ሐምሌ 15 ቀን 2017ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
==================
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አመራርና ሰራተኞች በ2018 ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡ ውይይቱን የድርጅቱን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢንጂነር መዓዛ አበራ በንግግር የከፈቱት ሲሆን
እቅዱን ያቀረቡት የሰርቲፊኬሽንና የኢንስፔክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አቤል አንበርብር ናቸው። የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ከ2018 ዕቅድ ጋር በንፅፅር የቀረበ ሲሆን እቅዱን ተፈፃሚ ለማድረግ የሁሉንም ርብርብ እንደሚጠይቅ ተመላክቷል።
በቀረበው ሀገራዊ እቅድ ላይም ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በተጨማሪም የድርጅቱን ዕቅድ ከሀገራዊ የልማት ዕቅድ ጋር በማቀናጀት ቀርቧል፡፡
በመጨረሻም የተለያዩ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ ክብርት ኢንጂነር መዓዛ አበራ ፕሮግራሙን አጠቃለዋል።


Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።