ኢተምድ ለሁለት ድርጅቶች የሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
ሰኔ 17 ቀን 2017ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
====================
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለሳብያን ቤዝ ሜታል ኢንጂኔሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማ (ISO 9001 Quality Management system) የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት እንዲሁም ለአለማየሁ ንጉሴ ሜታል ፓኬጂንግ (ISO 9001 Quality Management system) የጥራት የሥራ አመራር ሥርዓትና (ISO 14001 Environment Management System) የአከባቢ ስራ አመራር ስርዓት ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን ማሟላታቸውን በተከናወነላቸው የኦዲት ሂደት ተገምግሞ የተሰጣቸው ሲሆን ሰርቲፊኬቱን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ለድርጅቶቹ የሥራ ኃላፊዎች አስረክበዋል፡፡
በሰርቲፊኬቱ ርክክብ ወቅት የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂኔር መአዛ አበራ ዓለም አቀፍ የስራ አመራር ስርዓት ሰርቲፊኬት ማግኘታቹ ለሚትሰጡት አገልግሎት ሆነ ለሚታመርቱት ምርት በሀገር ውስጥና በዓለምአቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ተመራጭ እንዲትሆኑ አስቻይ መሆኑን አብራርቷል ። አክለውም የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ለድርጅቶቹ ተወካዮች ሰፊ ገለፃ ያደረጉላቸው ሲሆን በመጨረሻም የእንኳን ደስአላችሁ መልእክትም አስተላልፈዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።