ግንቦት 14 ቀን 2017ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
===============
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለካዲስኮ ቀለምና ማጣበቂያ ኢንዱስትሪ አ.ማ የሥራ ቦታ ጤና እና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት (ISO 45001) ሰርተፊኬት ሰጠ።
አክስዮን ማህበሩ ሰርተፍኬቱን ያገኘው ለሥራ አመራር ሥርዓት የተቀመጡ ዓለም አቀፍ መመዘኛ መስፈርቶችን ማሟላቱን ኢተምድ ባካሄደው የኦዲት ግምገማ በመረጋገጡ ነው። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ ለአክስዮን ማህበሩ የእንኳን ደስአላችሁ መልእክት እና በቀጣይ በሌሎች የአገልግሎት ዓይነቶች በጋራ ለመስራት ኢተምድ ዝግጁ መሆኑን በመግለፅ ሰርተፊኬቱን ለአክስዮን ማህበሩ የሥራ ኃላፊዎች አስረክበዋል።


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።