ግንቦት 07 ቀን 2017ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
===============
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የ (ISO 9001) የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
ባለስልጣን መ/ቤቱ ሰርተፍኬቱን ያገኘው ለሥራ አመራር ሥርዓቱ የተቀመጡ ዓለም አቀፍ መመዘኛ መስፈርቶችን ማሟላቱን ኢተምድ ባካሄደው የኦዲት ግምገማ በመረጋገጡ ነው። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ለባለስልጣኑ የሥራ ኃላፊዎች የእንኳን ደስአላችሁ መልእክት እና በቀጣይ በሌሎች የአገልግሎት ዓይነቶች በጋራ ለመስራት ኢተምድ ዝግጁ መሆኑን በመግለፅ ሰርተፊኬቱን ለባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብዱልበር ሸምሱ አስረክበዋል።



Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።