ግንቦት 07 ቀን 2017ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
===============
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የ (ISO 9001) የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
ባለስልጣን መ/ቤቱ ሰርተፍኬቱን ያገኘው ለሥራ አመራር ሥርዓቱ የተቀመጡ ዓለም አቀፍ መመዘኛ መስፈርቶችን ማሟላቱን ኢተምድ ባካሄደው የኦዲት ግምገማ በመረጋገጡ ነው። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ለባለስልጣኑ የሥራ ኃላፊዎች የእንኳን ደስአላችሁ መልእክት እና በቀጣይ በሌሎች የአገልግሎት ዓይነቶች በጋራ ለመስራት ኢተምድ ዝግጁ መሆኑን በመግለፅ ሰርተፊኬቱን ለባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብዱልበር ሸምሱ አስረክበዋል።



Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሥራ አመራሮችና ሰራተኞች በሰበታ ሀዋስ ወረዳ ሁለተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አከናወኑ፡፡
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሥራ አመራሮችና ሰራተኞች በሰበታ ሀዋስ ወረዳ ሁለተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አከናወኑ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢተምድ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትን የሥራ እንቅስቃሴ ጎበኙ፡፡