
ግንቦት 07 ቀን 2017ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
===============
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የ (ISO 9001) የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
ባለስልጣን መ/ቤቱ ሰርተፍኬቱን ያገኘው ለሥራ አመራር ሥርዓቱ የተቀመጡ ዓለም አቀፍ መመዘኛ መስፈርቶችን ማሟላቱን ኢተምድ ባካሄደው የኦዲት ግምገማ በመረጋገጡ ነው። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ለባለስልጣኑ የሥራ ኃላፊዎች የእንኳን ደስአላችሁ መልእክት እና በቀጣይ በሌሎች የአገልግሎት ዓይነቶች በጋራ ለመስራት ኢተምድ ዝግጁ መሆኑን በመግለፅ ሰርተፊኬቱን ለባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብዱልበር ሸምሱ አስረክበዋል።
Related Posts
የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች በኢተምድ የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄዱ፡፡
ኢተምድ ከደብረብርሃን ዪኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡
ኢተምድ ለደብረብርሃን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የISO 9001 የጥራት የሥራ አመራር ሥርዓት ሰርቲፊኬት ሰጠ።