ግንቦት 06 ቀን 2017ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
==================
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት (ኢተምድ) የሥራ ኃላፊዎች ከInternational Center of Insect Physiology and Ecology Ethiopia (ICIPE) ካንትሪ ዳይሬክተር ዶ/ር ታደለ ተፈራ ጋር የማር ምርት ጥራትን በማስጠበቅ ዙሪያ ተወያዩ፡፡ በማር ምርት ላይ የጥራት ፍተሻ አቅምን በሀገር ውስጥ በመገንባት ዘርፉን ለማሳደግ ያለመ ፕሮጀክት አካል የሆነው ይህ ውይይት ኢተምድ ቀድሞ በማር ምርት ላይ እየሰጣቸው የሚገኙ የፍተሻ፣ የኢንስፔክሽንና የሰርቲፊኬሽን አገልግሎቶችን ወደላቀ ደረጃ በማሸጋገር ዘርፉን ለመደገፍ ለማስቻል ባለሙያዎችን በማብቃት፣በፍተሻ ግብዓት አቅርቦት፣አሰራር ሥርዓትን በማሻሻል እና አገልግሎቱን በማስተዋወቅ መስኮች ለኢተምድ ድጋፍ በማድረግ ሥራዎችን በጋራ መስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡ በወይይቱ ወቅት የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መአዛ አበራ ኢተምድ እየሠጣቸው የሚገኘውን የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃ አድርገውላቸዋል፡፡


Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።