የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለሸገር ዳቦና ዱቄት ፋብሪካ በአራት የስራ አመራር ስርዓት (ISO 9001) የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት፣ (ISO14001) የአካባቢ ስራ አመራር ስርዓት፣(ISO 45001) የስራ ቦታ ጤና እና ደህንነት ስራ አመራር ስርዓት እና (ISO 22000) የምግብ ደህንነት ስራ አመራር ስርዓት የተቀናጀ የሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
ድርጅቱ ሰርተፍኬቱን ያገኘው በአራቱም የሥራ አመራር ሥርዓት የተቀመጡ ዓለም አቀፍ መመዘኛ መስፈርቶችን ማሟላቱን ኢተምድ ባካሄደው የኦዲት ግምገማ በማረጋገጡ ነው። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ለድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎች የኢተምድ አገልግሎቶች ማብራርያና የእንዃን ደስአላችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን ሰርተፊኬቱን ለድርጅቱ ስራ ሃላፊዎች አስረክበዋል።


Related Posts
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢተምድ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትን የሥራ እንቅስቃሴ ጎበኙ፡፡
የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሥራ እንቅስቃሴ ገመገሙ፡፡
ኢተምድ በአዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)