ኢተምድ ለሁለት ድርጅቶች የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።

የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለወ/ሮ ስኂን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ለኤልኤም ትሬዲንግ ግሩፕ ኃ/የተ/የግ/ማ (ISO 9001፡2015) የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡
ድርጅቶቹ ሰርተፍኬቱን ያገኙት ለጥራት የሥራ አመራር ሥርዓት የተቀመጡ ዓለም አቀፍ መመዘኛ መስፈርቶችን ማሟላታቸውን በተከናወነላቸው የኦዲት ሂደት ተረጋግጦ ሲሆን ሰርቲፊኬቱን የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ለድርጅቶቹ የሥራ ኃላፊዎች አስረክበዋል፡፡