
በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ የተመሩ የባለስልጣን መ/ቤቱ አመራርና ሠራተኞች በዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች የተደራጁትን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዘጠኝ የፍተሻ ላብራቶሪዎች ጎብኝተዋል፡፡ የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ኢተምድ የህብረተሰቡንና የአካባቢን ጤና እና ደህንነት ለማስጠበቅ ድርጅቱ የሚሰጣቸውን የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃና ማብራሪያ አድርገውላቸዋል፡፡
ጉብኝቱ እንደ ሀገር ጥራት ያለው ምርትና አገልግሎትን በማቅረብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆንና ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገትን ለማረጋገጥ ከጥራት አንፃር በድርጅቱ አገልግሎቶች ዙሪያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ግንዛቤ ለማሳደግ ዘርፉ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ማድረግንና ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠርን አላማው ያደረገ ነው፡፡
Related Posts
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢተምድ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡
ኢተምድ ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 7ኛ ዓመት አስመልክቶ ውይይት አካሄደ።