በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ የተመሩ የባለስልጣን መ/ቤቱ አመራርና ሠራተኞች በዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች የተደራጁትን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዘጠኝ የፍተሻ ላብራቶሪዎች ጎብኝተዋል፡፡ የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ኢተምድ የህብረተሰቡንና የአካባቢን ጤና እና ደህንነት ለማስጠበቅ ድርጅቱ የሚሰጣቸውን የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃና ማብራሪያ አድርገውላቸዋል፡፡
ጉብኝቱ እንደ ሀገር ጥራት ያለው ምርትና አገልግሎትን በማቅረብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆንና ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገትን ለማረጋገጥ ከጥራት አንፃር በድርጅቱ አገልግሎቶች ዙሪያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ግንዛቤ ለማሳደግ ዘርፉ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ማድረግንና ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠርን አላማው ያደረገ ነው፡፡



Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።