
በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ የተመሩ የባለስልጣን መ/ቤቱ አመራርና ሠራተኞች በዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች የተደራጁትን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዘጠኝ የፍተሻ ላብራቶሪዎች ጎብኝተዋል፡፡ የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ኢተምድ የህብረተሰቡንና የአካባቢን ጤና እና ደህንነት ለማስጠበቅ ድርጅቱ የሚሰጣቸውን የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃና ማብራሪያ አድርገውላቸዋል፡፡
ጉብኝቱ እንደ ሀገር ጥራት ያለው ምርትና አገልግሎትን በማቅረብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆንና ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገትን ለማረጋገጥ ከጥራት አንፃር በድርጅቱ አገልግሎቶች ዙሪያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ግንዛቤ ለማሳደግ ዘርፉ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ማድረግንና ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠርን አላማው ያደረገ ነው፡፡
Related Posts
3ኛው የአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት ጉባኤ ተሳታፊዎች የኢተምድ ላቦራቶሪዎችን ጎበኙ።
የኢተምድ አመራርና ሠራተኞች በ2018 ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡
የኢተምድ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ የችግኝ ተከላ መርሃግብር አካሄዱ።