ከመጋቢት 4‐8/2017 ዓ.ም “የኢትዮጵያን ይግዙ” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው 14ኛው የኢትዮ-ቻምበር ዓለም ዓቀፍ የንግድ ትርዒት በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማእከል ተከፍቷል፡፡ የንግድ ትርዒቱ በኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት እና በኢፌዴሪ ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በጋራ የተዘጋጀ ሲሆን ለአምስት ተከታታይ ቀናት ለህዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡ የንግድ ትርዒቱን የከፈቱት የኢፌዴሪ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶክተር ካሳሁን ጎፌ ንግድ ትርዒቱ የሀገር ውስጥ ምርትና አገልግሎቶች የሚተዋወቁበትና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ልምድ የሚለዋወጡበት እንደሚሆን ገልጸዋል።
በንግድ ትርኢቱ ኢተምድን ጨምሮ በተለያየ ዘርፍ የተሰማሩ ከ200 መቶ በላይ የአገር ዉስጥ አምራቾች እና የዉጭ ድርጅቶች ተሳታፊ ሆነዋል። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅትም የምርትና አገልግሎቶችን ጥራትን የመጠበቅ እና የማስጠበቅ አስፈላጊነትን፣ጥራትን ለማስጠበቅ የሚሰጣቸውን የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች፣ የድርጅቱን ተግባርና ኃላፊነት መሰረተ ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ በመስጠት ድርጅቱን በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል።


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።