የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ሠራተኞች እና ሥራ አመራሮች 129ኛውን የዓድዋ ድል በዓል “ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል” በሚል መሪ ቃል የካቲት 20 ቀን 2017 ዓ.ም አከበሩ፡፡ በዓሉን የተመለከተ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መዓዛ አበራ ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል መሆኑንና መላው ሠራተኛ በተሰማራበት የሥራ መስክ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ እንደተቋም ከአገልግሎት አሰጣጥ አንፃር ከብልሹ አሰራር የፀዳ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ድርጅቱ የተጣለበትን የሀገር ኢኮኖሚ የመደገፍ ተልዕኮ በብቃት እንዲወጣ ትጋትና ጥንካሬን በመላበስ ለሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት በመሥራት አባቶቻችን ሀገርን እንደጠበቁ እኛም የሀገር ሠላምን ልንጠብቅ ለልጆቻችን እዳን ሳይሆን ምንዳን ልናወርስ ይገባል በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የዓድዋ የድል በዓል በሀገር ዓቀፍ ደረጃ የካቲት 23 ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡


Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።