ለጨጨሆ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማ የምግብ ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት( ISO 22000:2018 Food safety Management system) እና winner pipes የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት (ISO 9001:2015 Quality Management system) ሰርቲፊኬት ከኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢንጂኔር መአዛ አበራ ተረክቧል።
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢንጂኔር መአዛ አበራ ዓለም አቀፍ የስራ አመራር ስርዓት ሰርቲፊኬት ማግኘታቹ ለሚትሰጡት አገልግሎት ሆነ ለሚታመርቱት ምርት በሀገር ውስጥና በዓለምአቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ተመራጭ እንዲትሆኑ አስቻይ መሆኑን በርክክቡ ወቅት አብራርቷል አክለውም የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ሰርቲፋይድ ለሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች ሰፊ ገለፃ ያደረጉላቸው ሲሆን በመጨረሻም የእንኳን ደስአላችሁ መልእክትም አስተላልፏል።
የሁለቱም ሰርቲፋይድ የሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች በበኩላቸው ለጥራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ዓለምአቀፍ ሥራ አመራር ሥርዓት አስፈላጊውን መስፈርት አሟልተን ሰርቲፋይድ በመሆናችን በዓለምአቀፍ ደረጃ ተመራጭ እንድንሆን ወሳኝ ሚና ስለሚጫወት እና ድርጅቱም ላደረገው ሙያዊ የአዲት ስራ እጅግ ደስተኞች መሆናቸውን የገለፁ ሲሆን አክለውም ሰርተፍኬቱ ለቀጣይ ስኬት አነሳሽ እንደሆነም አብራርተዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።