ማማ ወተት በሚለው የብራንድ ስሙ የሚታወቀው ሰበታ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማ የምግብ ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት( ISO 22000:2018 Food safety Management system) እና የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት (ISO 9001:2015 Quality Management system) ሰርተፊኬት ከኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ተረክቧል።
የኢትዮጵያ ተስማሚነት እና ምዘና ድርጅት የኦፕሬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አቤል አንበርብር በጥራት ለሚያመርቱ አምራቾች እውቅና መስጠት በሀገር ውስጥና በዓለምአቀፍ ደረጃ የገበያ ተወዳዳሪነትን ያጠናክራል ሲሉ በርክክቡ ወቅት ተናግረዋል።
የሰበታ አግሮ ኢንዱስትሪ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ሳራ ሀሰን በበኩላቸው ሰበታ አግሮ ኢንዱስትሪ ለምግብ ደህንነት እና ጥራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ዓለምአቀፍ የምግብ ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት (ISO 22000:2018 Food safety Management system) እና ዓለምአቀፍ የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት (ISO 9001:2015 Quality Management system) ሰርቲፋይድ መሆኑን የገለፁ ሲሆን አክለውም ሰርተፍኬቱ ለቀጣይ ስኬት አነሳሽ እንደሆነ ተናግረዋል::


Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሥራ አመራሮችና ሰራተኞች በሰበታ ሀዋስ ወረዳ ሁለተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አከናወኑ፡፡
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሥራ አመራሮችና ሰራተኞች በሰበታ ሀዋስ ወረዳ ሁለተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አከናወኑ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢተምድ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትን የሥራ እንቅስቃሴ ጎበኙ፡፡