
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን (ISO 9001) የጥራት ሥራ አመራር ሥርአት ሰርተፍኬት ሰጥቷል፡፡ ኮርፖሬሽኑ የጥራት ሥራ አመራር ሥርአት የሚጠይቀውን የዓለም አቀፍ መመዘኛዎች በተከናወነውን የኦዲት ሂደት መስፈርቶችን በማሟላታቸው ሰርተፍኬቱ ተሰጣቷቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ ለኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ሰርተፊኬቱን በሰጡበት ወቅት የእንኳን ደስአላችሁ መልእክትም አስተላልፈዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የኢፌድሪ የትርንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የቦርድ አባል ክቡር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
Related Posts
3ኛው የአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት ጉባኤ ተሳታፊዎች የኢተምድ ላቦራቶሪዎችን ጎበኙ።
የኢተምድ አመራርና ሠራተኞች በ2018 ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡
የኢተምድ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ የችግኝ ተከላ መርሃግብር አካሄዱ።