የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን (ISO 9001) የጥራት ሥራ አመራር ሥርአት ሰርተፍኬት ሰጥቷል፡፡ ኮርፖሬሽኑ የጥራት ሥራ አመራር ሥርአት የሚጠይቀውን የዓለም አቀፍ መመዘኛዎች በተከናወነውን የኦዲት ሂደት መስፈርቶችን በማሟላታቸው ሰርተፍኬቱ ተሰጣቷቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ ለኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ሰርተፊኬቱን በሰጡበት ወቅት የእንኳን ደስአላችሁ መልእክትም አስተላልፈዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የኢፌድሪ የትርንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የቦርድ አባል ክቡር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።