ኢተምድ ለሦስት ድርጅቶች የሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።

የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለኢላይት ኢንጂነሪንግ ሶሉሽንስ ኃ/የተ/የግ/ማ (ISO 9001፡2015) የጥራት ሥራ አመራር ሥርአት እና (ISO 45001) የሥራ ቦታ ጤናና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት) 2 ሰርተፊኬት፣ ለናሽናል ማይኒንግ ኮርፖሬሽን ኃ/የተ/የግ/ማ እና ለዋዳ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማ (ISO 9001፡2015) የጥራት የሥራ አመራር ሥርዓት ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን ማሟላታቸውን በተከናወነላቸው የኦዲት ሂደት ተገምግሞ የተሰጣቸው ሲሆን ሰርቲፊኬቱን የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ለድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎች አስረክበዋል፡፡