ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ የትምህርት ክፍሎች የተውጣጡ ዲኖች፣ ከፍተኛ የሥራ አመራሮች እና የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች የተገኙበት የልኡካን ቡድን በዘመናዊ የፍተሻ ቴክኖሎጂዎች የተደራጁትን የኢተምድ ላቦራቶሪዎች ጎበኙ፡፡ በጉብኝታቸው በሀገር ውስጥ የሚመረቱና ከውጪ የሚመጡ ምርቶችን ጥራት የሚያረጋግጡ በዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች የተደራጁ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዘጠኝ የፍተሻ ላቦራቶሪዎች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ኢተምድ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች እና የሥራ እንቅስቃሴውን በተለይም ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በምርምርና አፕላይድ ሪሰርች ዘርፍ እና ተማሪዎችን በኢንተርሺፕ ተቀብሎ በተግባር ማብቃትና ማሰልጠን ላይ ኢተምድ ከትምህርት ተቋማቱ ጋር በጋራ እየሰራባቸው በሚገኝባቸው መስኮችና አገልግሎቶች ላይ ገለፃና ማብራሪያ አድርገውላቸዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።