
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት እና የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎቶችን በዓለም አቀፍ የአሰራር ሥርዓት መሰረት ተግባራዊ ለማድረግ በትብብር ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡ የስምምነቱን ሰነድ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መአዛ አበራ እና የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ወንድሙ ደንቡ ፈርመዋል።
ስምምነቱ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎቶችን በዓለም-አቀፍ አሰራር ሥርዓት መሰረት ተግባራዊ ለማድረግ የተደረገ ሲሆን የሎጅስቲክስ አገልግሎት በሀገራዊ እና ዓለም-አቀፋዊ ደረጃዎች መስፈርት መሰረት ጥራቱን በማረጋገጥ፣ተቋማዊ ልምድን ፣ሙያዊና ቁሳዊ ሀብትን አስተባብሮ በጋራ በመስራት የአገልግሎት ጥራት በማረጋገጥ የጥራት ጉድለት ሊያስከትል የሚችለውን ዘርፈ-ብዙ አሉታዊ ጉዳት በማስቀረት የኢንዱስትሪው ውጤታማነት፣ ቅልጥፍና እና ተወዳዳሪነት ላይ የሚኖረው ፋይዳ ትልቅ እንደሆነ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል፡፡
Related Posts
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አመራርና ሠራተኞች ኢተምድን ጎበኙ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢተምድ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡