የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት እና የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎቶችን በዓለም አቀፍ የአሰራር ሥርዓት መሰረት ተግባራዊ ለማድረግ በትብብር ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡ የስምምነቱን ሰነድ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መአዛ አበራ እና የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ወንድሙ ደንቡ ፈርመዋል።
ስምምነቱ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎቶችን በዓለም-አቀፍ አሰራር ሥርዓት መሰረት ተግባራዊ ለማድረግ የተደረገ ሲሆን የሎጅስቲክስ አገልግሎት በሀገራዊ እና ዓለም-አቀፋዊ ደረጃዎች መስፈርት መሰረት ጥራቱን በማረጋገጥ፣ተቋማዊ ልምድን ፣ሙያዊና ቁሳዊ ሀብትን አስተባብሮ በጋራ በመስራት የአገልግሎት ጥራት በማረጋገጥ የጥራት ጉድለት ሊያስከትል የሚችለውን ዘርፈ-ብዙ አሉታዊ ጉዳት በማስቀረት የኢንዱስትሪው ውጤታማነት፣ ቅልጥፍና እና ተወዳዳሪነት ላይ የሚኖረው ፋይዳ ትልቅ እንደሆነ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል፡፡




Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።