በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ የተመራ የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ አመራሮች እና የተጠሪ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች የተገኙበት የልኡካን ቡድን በዘመናዊ የፍተሻ ቴክኖሎጂዎችና ባለሙያዎች የተደራጀውን የጥራት መንደር ጎበኙ፡፡ በጉብኝታቸው ጥራትን የሚያረጋግጡ ዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች የታጠቁ የላብራቶሪና የቢሮ ግንባታ የያዘ እና በብቁ ባለሙያዎች የተደራጀውን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የፍተሻ ላብራቶሪዎች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ በተለይም በጥራት መንደሩ የሚገኙ ተቋማት በጤናው ዘርፍ አገልግሎት ላይ የሚውሉ ግብዓቶችና የተለያዩ ምርቶችን ጥራት ከማረጋገጥ አንፃር ኢተምድ እየሰጣቸው ስለሚገኘው አገልግሎቶች ገለፃና ማብራሪያ አድርገውላቸዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።