
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለኤዲዩ ኮሙኒኬሽን ሰርቪስ ኃ/የተ/የግ/ማ የተቀናጀ የሥራ አመራር ሥርዓት (በጥራት ሥራ አመራር ሥርአት፣በአካባቢ ሥራ አመራር ሥርዓት እና በሥራ ቦታ ጤናና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት) ሰርተፊኬት ሰጠ፡፡ ድርጅቱ የተቀናጀ የሥራ አመራር ሥርዓት ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን ማሟላቱን በተከናወነለት የኦዲት ሂደት ተገምግሞ የተሰጠው ሲሆን ሰርቲፊኬቱን የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ለድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አስረክበዋል፡፡ ኤዲዩ ኮሙኒኬሽን ሰርቪስ ኃ/የተ/የግ/ማ በቴሌኮም እና በአይሲቲ መሰረተ ልማት ሥራዎች ላይ የተሰማራ ድርጅት ነው፡፡
Related Posts
3ኛው የአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት ጉባኤ ተሳታፊዎች የኢተምድ ላቦራቶሪዎችን ጎበኙ።
የኢተምድ አመራርና ሠራተኞች በ2018 ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡
የኢተምድ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ የችግኝ ተከላ መርሃግብር አካሄዱ።