የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለኤዲዩ ኮሙኒኬሽን ሰርቪስ ኃ/የተ/የግ/ማ የተቀናጀ የሥራ አመራር ሥርዓት (በጥራት ሥራ አመራር ሥርአት፣በአካባቢ ሥራ አመራር ሥርዓት እና በሥራ ቦታ ጤናና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት) ሰርተፊኬት ሰጠ፡፡ ድርጅቱ የተቀናጀ የሥራ አመራር ሥርዓት ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን ማሟላቱን በተከናወነለት የኦዲት ሂደት ተገምግሞ የተሰጠው ሲሆን ሰርቲፊኬቱን የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ ለድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አስረክበዋል፡፡ ኤዲዩ ኮሙኒኬሽን ሰርቪስ ኃ/የተ/የግ/ማ በቴሌኮም እና በአይሲቲ መሰረተ ልማት ሥራዎች ላይ የተሰማራ ድርጅት ነው፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።