
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አጽቀ ስላሴ በቅርቡ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀውን እና በዘመናዊ የፍተሻ ቴክኖሎጂዎችና ባለሙያዎች የተደራጀውን የጥራት መንደር ጎበኙ፡፡ ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው በዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች እና ባለሙያዎች የተደራጀውንና ደረጃቸውን የጠበቁትን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዘጠኝ የፍተሻ ላብራቶሪዎች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር መዓዛ አበራ እንዲሁም የድርጅቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ኢተምድ እየሰጣቸው ስለሚገኘው አገልግሎቶች ገለፃና ማብራሪያ አድርገውላቸዋል፡፡
Related Posts
ኢተምድ ለኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
የኢተምድ የሥራ ኃላፊዎች ከICIPE የሥራ ኃላፊዎች ጋር የማር ምርት ጥራት ማስጠበቅን በተመለከተ ተወያዩ ።
ኢተምድ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡