
ሀገራችን ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ቀዳሚ የጥራት ማዕከል የሚያደርጋትና የምርት ጥራትን ለማረጋገጥና ከዘርፉ ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስችላት የተለያዩ የጥራት መሠረተ ልማቶችን በአንድ ቦታ ላይ አካቶ የያዘ የጥራት መንደር በዘመናዊ የፍተሻ ቴክኖሎጂዎች ተደራጅቶ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን ተመርቋል፡፡ በዛሬው እለት ከተለያዩ መ/ቤቶች የተውጣጡ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ አምራች ድርጅቶች እና የተለያዩ ማህበራት በጥራት መንደሩ በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል፡፡ በጉብኝታቸውም ከውጪ ሀገራት የሚገቡ እና በሀገራችን የሚመረቱ የተለያዩ ምርቶች የጥራት ደረጃ የሚፈተሽባቸውን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ላብራቶሪዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡ ፡በድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቋሙ የምርትና አገልግሎቶችን ጥራት ከማስጠበቅ አንፃር እየሰጣቸው የሚገኘውን አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃም ተደርጎላቸዋል፡፡
Related Posts
3ኛው የአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት ጉባኤ ተሳታፊዎች የኢተምድ ላቦራቶሪዎችን ጎበኙ።
የኢተምድ አመራርና ሠራተኞች በ2018 ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡
የኢተምድ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ የችግኝ ተከላ መርሃግብር አካሄዱ።