ሀገራችን ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ቀዳሚ የጥራት ማዕከል የሚያደርጋትና የምርት ጥራትን ለማረጋገጥና ከዘርፉ ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስችላት የተለያዩ የጥራት መሠረተ ልማቶችን በአንድ ቦታ ላይ አካቶ የያዘ የጥራት መንደር በዘመናዊ የፍተሻ ቴክኖሎጂዎች ተደራጅቶ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን ተመርቋል፡፡ በዛሬው እለት ከተለያዩ መ/ቤቶች የተውጣጡ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ አምራች ድርጅቶች እና የተለያዩ ማህበራት በጥራት መንደሩ በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል፡፡ በጉብኝታቸውም ከውጪ ሀገራት የሚገቡ እና በሀገራችን የሚመረቱ የተለያዩ ምርቶች የጥራት ደረጃ የሚፈተሽባቸውን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ላብራቶሪዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡ ፡በድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቋሙ የምርትና አገልግሎቶችን ጥራት ከማስጠበቅ አንፃር እየሰጣቸው የሚገኘውን አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃም ተደርጎላቸዋል፡፡


Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።