
ሀገራችን ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ቀዳሚ የጥራት ማዕከል የሚያደርጋትና የምርት ጥራትን ለማረጋገጥና ከዘርፉ ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስችላት የተለያዩ የጥራት መሠረተ ልማቶችን በአንድ ቦታ ላይ አካቶ የያዘ የጥራት መንደር በዘመናዊ የፍተሻ ቴክኖሎጂዎች ተደራጅቶ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን ተመርቋል፡፡ በዛሬው እለት ከተለያዩ መ/ቤቶች የተውጣጡ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ አምራች ድርጅቶች እና የተለያዩ ማህበራት በጥራት መንደሩ በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል፡፡ በጉብኝታቸውም ከውጪ ሀገራት የሚገቡ እና በሀገራችን የሚመረቱ የተለያዩ ምርቶች የጥራት ደረጃ የሚፈተሽባቸውን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ላብራቶሪዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡ ፡በድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቋሙ የምርትና አገልግሎቶችን ጥራት ከማስጠበቅ አንፃር እየሰጣቸው የሚገኘውን አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃም ተደርጎላቸዋል፡፡
Related Posts
ኢተምድ ለኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
የኢተምድ የሥራ ኃላፊዎች ከICIPE የሥራ ኃላፊዎች ጋር የማር ምርት ጥራት ማስጠበቅን በተመለከተ ተወያዩ ።
ኢተምድ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡