
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሠራተኞች በዘመናዊ የፍተሻ ቴክኖሎጂዎች ተደራጅቶ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን የተመረቀውን የጥራት መንደር ጎብኝተዋል፡፡ የጥራት መንደሩ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅትን፣የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩትን የኢትዮጵያ ስነ-ልክ ኢንስቲትዩትን፣ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎትን እና የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣንን ያካተተ ነው፡፡
በጉብኝታቸውም የተቀናጀና ደረጃውን የጠበቀ የጥራት ፍተሻ አገልግሎት ለመስጠት በዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች የተደራጁትን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዘጠኝ ላብራቶሪዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቋሙ የምርትና አገልግሎቶችን ጥራት ከማስጠበቅ አንፃር እየሰጣቸው የሚገኘውን አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡
Related Posts
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አመራርና ሠራተኞች ኢተምድን ጎበኙ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢተምድ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡