የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሠራተኞች በዘመናዊ የፍተሻ ቴክኖሎጂዎች ተደራጅቶ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን የተመረቀውን የጥራት መንደር ጎብኝተዋል፡፡ የጥራት መንደሩ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅትን፣የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩትን የኢትዮጵያ ስነ-ልክ ኢንስቲትዩትን፣ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎትን እና የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣንን ያካተተ ነው፡፡
በጉብኝታቸውም የተቀናጀና ደረጃውን የጠበቀ የጥራት ፍተሻ አገልግሎት ለመስጠት በዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች የተደራጁትን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዘጠኝ ላብራቶሪዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቋሙ የምርትና አገልግሎቶችን ጥራት ከማስጠበቅ አንፃር እየሰጣቸው የሚገኘውን አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡


Related Posts
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢተምድ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትን የሥራ እንቅስቃሴ ጎበኙ፡፡
የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሥራ እንቅስቃሴ ገመገሙ፡፡
ኢተምድ በአዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)