የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሠራተኞች በዘመናዊ የፍተሻ ቴክኖሎጂዎች ተደራጅቶ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን የተመረቀውን የጥራት መንደር ጎብኝተዋል፡፡ የጥራት መንደሩ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅትን፣የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩትን የኢትዮጵያ ስነ-ልክ ኢንስቲትዩትን፣ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎትን እና የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣንን ያካተተ ነው፡፡
በጉብኝታቸውም የተቀናጀና ደረጃውን የጠበቀ የጥራት ፍተሻ አገልግሎት ለመስጠት በዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች የተደራጁትን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዘጠኝ ላብራቶሪዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቋሙ የምርትና አገልግሎቶችን ጥራት ከማስጠበቅ አንፃር እየሰጣቸው የሚገኘውን አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።