የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሠራተኞች በዘመናዊ የፍተሻ ቴክኖሎጂዎች ተደራጅቶ በቅርቡ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን የተመረቀውን የጥራት መንደር ጎብኝተዋል፡፡ የጥራት መንደሩ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅትን፣የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩትን የኢትዮጵያ ስነ-ልክ ኢንስቲትዩትን፣ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎትን እና የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣንን ያካተተ ነው፡፡
በጉብኝታቸውም የተቀናጀና ደረጃውን የጠበቀ የጥራት ፍተሻ አገልግሎት ለመስጠት በዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች የተደራጁትን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዘጠኝ ላብራቶሪዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የድርጅቱ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተቋሙ የምርትና አገልግሎቶችን ጥራት ከማስጠበቅ አንፃር እየሰጣቸው የሚገኘውን አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡


Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።