
ኢተምድ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 6,823 የአገልግሎት ጥያቄዎችን በማስተናገድ የጥራት ማረጋገጥ ሥራዎችን አከናውኗል፡፡
መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
====================
ኢተምድ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት 6,823 አገልግሎቶችን በላብራቶር ፍተሻ፣በውጪና አገር ውስጥ ምርት ኢንስፔክሽን፣ በሠርተፊኬሽን እንዲሁም በጁቡቲ ወደብ በኩል ለ445,651.65 ሜ/ቶን የአፈር ማዳበሪያ እና ለ7,193,952.00 የምግብ ዘይት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ሰጥቷል፡፡
ኢተምድ ዋና መ/ቤቱን አዲስ አበባ በማድረግ በ9 የተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ቅርንጫፍ በመክፈት እንዲሁም በውጭ ሀገር በጅቡቲ ወደብና በኬንያ ላሙ ወደብ የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶችን በመስጠት ሁሉን አቀፍ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገቶች አስተማማኝ መሠረት እንዲኖራቸው እና ቀጣይነታቸውን በማረጋገጥ አገራዊ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት በሚደረገው ርብርብ ሀላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛል፡፡
Related Posts
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አመራርና ሠራተኞች ኢተምድን ጎበኙ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢተምድ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡