ኢተምድ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 6,823 የአገልግሎት ጥያቄዎችን በማስተናገድ የጥራት ማረጋገጥ ሥራዎችን አከናውኗል፡፡
መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
====================
ኢተምድ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት 6,823 አገልግሎቶችን በላብራቶር ፍተሻ፣በውጪና አገር ውስጥ ምርት ኢንስፔክሽን፣ በሠርተፊኬሽን እንዲሁም በጁቡቲ ወደብ በኩል ለ445,651.65 ሜ/ቶን የአፈር ማዳበሪያ እና ለ7,193,952.00 የምግብ ዘይት ኢንስፔክሽን አገልግሎት ሰጥቷል፡፡
ኢተምድ ዋና መ/ቤቱን አዲስ አበባ በማድረግ በ9 የተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ቅርንጫፍ በመክፈት እንዲሁም በውጭ ሀገር በጅቡቲ ወደብና በኬንያ ላሙ ወደብ የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶችን በመስጠት ሁሉን አቀፍ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገቶች አስተማማኝ መሠረት እንዲኖራቸው እና ቀጣይነታቸውን በማረጋገጥ አገራዊ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት በሚደረገው ርብርብ ሀላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።