የኢፌዲሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአ እምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት የማአድ ማጋራት ፕሮግራም አካሂዷል፡፡
ጳጉሜ 4 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
========================
የኢፌዲሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ጳጉሜ 4 የኅብር ቀንን ምክንያት በማድረግ በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአ እምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት የማአድ ማጋራት የምሳ ፕሮግራም አካሂዷል፡፡
በፕሮግራሙ የተገኙት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ እንደ ሀገር የመስጠት ልምምድ ሊኖረን እንደሚገባ በመግለጽ በመስጠት የሚጎድል ነገር የለም ብለዋል፡፡ የመረዳዳት ባህልን ማዳበር እንደሚገባም አስረድተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የማነጅመንት አባላትም ጳጉሜ 4 የኅብር ቀን “ህብራችን ለሰላማችን” “አብረን ነበርን አብረን እንኖራለን” በሚሉ መሪ ሀሳቦች እለቱን ከሚኒስቴር መ/ቤቱ እና ተጠሪ ተቋማት በጋራ በመሆን በመቄዶንያየአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘትከ 7,500 በላይ ተረጂዎች ማዕድ የማጋራት እና ልዩ ልዩ ድጋፎችን በማድረግ እለቱን አክብረዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።