የኢፌዲሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአ እምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት የማአድ ማጋራት ፕሮግራም አካሂዷል፡፡
ጳጉሜ 4 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
========================
የኢፌዲሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ጳጉሜ 4 የኅብር ቀንን ምክንያት በማድረግ በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአ እምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት የማአድ ማጋራት የምሳ ፕሮግራም አካሂዷል፡፡
በፕሮግራሙ የተገኙት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ እንደ ሀገር የመስጠት ልምምድ ሊኖረን እንደሚገባ በመግለጽ በመስጠት የሚጎድል ነገር የለም ብለዋል፡፡ የመረዳዳት ባህልን ማዳበር እንደሚገባም አስረድተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የማነጅመንት አባላትም ጳጉሜ 4 የኅብር ቀን “ህብራችን ለሰላማችን” “አብረን ነበርን አብረን እንኖራለን” በሚሉ መሪ ሀሳቦች እለቱን ከሚኒስቴር መ/ቤቱ እና ተጠሪ ተቋማት በጋራ በመሆን በመቄዶንያየአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘትከ 7,500 በላይ ተረጂዎች ማዕድ የማጋራት እና ልዩ ልዩ ድጋፎችን በማድረግ እለቱን አክብረዋል፡፡


Related Posts
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢተምድ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትን የሥራ እንቅስቃሴ ጎበኙ፡፡
የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሥራ እንቅስቃሴ ገመገሙ፡፡
ኢተምድ በአዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)