
የኢፌዲሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአ እምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት የማአድ ማጋራት ፕሮግራም አካሂዷል፡፡
ጳጉሜ 4 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
========================
የኢፌዲሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ጳጉሜ 4 የኅብር ቀንን ምክንያት በማድረግ በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአ እምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት የማአድ ማጋራት የምሳ ፕሮግራም አካሂዷል፡፡
በፕሮግራሙ የተገኙት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ እንደ ሀገር የመስጠት ልምምድ ሊኖረን እንደሚገባ በመግለጽ በመስጠት የሚጎድል ነገር የለም ብለዋል፡፡ የመረዳዳት ባህልን ማዳበር እንደሚገባም አስረድተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የማነጅመንት አባላትም ጳጉሜ 4 የኅብር ቀን “ህብራችን ለሰላማችን” “አብረን ነበርን አብረን እንኖራለን” በሚሉ መሪ ሀሳቦች እለቱን ከሚኒስቴር መ/ቤቱ እና ተጠሪ ተቋማት በጋራ በመሆን በመቄዶንያየአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘትከ 7,500 በላይ ተረጂዎች ማዕድ የማጋራት እና ልዩ ልዩ ድጋፎችን በማድረግ እለቱን አክብረዋል፡፡
Related Posts
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አመራርና ሠራተኞች ኢተምድን ጎበኙ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢተምድ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡