የሠራተኞች የእውቅና አሰጣጥ መርሃ-ግብር ተከናወነ
ነሃሴ 20 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
============================
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በ2016 በጀት ዓመት ላስመዘገበው የላቀ ስኬት አስተዋፅኦ ላበረከቱ ፈፃሚ አመራርና ሠራተኞቹ በንግድና ቀጠናዊ ትስስርና ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ ፣ ክቡር አቶ እንዳለው መኮንን በንግድና ቀጠናዊ ትስስርና ሚኒስቴር የጥራት ማረጋገጫ ዘርፍ ሚ/ር ዲኤታ እና ክብርት ወ/ሮ ያስሚን ወሀብረቢ በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ትስስርና የወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚ/ር ዲኤታ በተገኙበት እንደ አስተዋፅኦ ደረጃቸው የምስጋና የምስክር ወረቀት እና የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ ይህ የእውቅና መርሃ ግብር በንግድና ቀጠናዊ ትስስርና ሚኒስቴር ሀሳብ አመንጪነት ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሄደ የሚገኘው አገር አቀፍ የንግድ ሳምንት አካል ሲሆን በእውቅና አሰጣጥ መርሃ- ግብሩ ላይ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ ሀገር የምትሻገረው ጎበዞቿን ማክበርና ማበረታታት ስትችል እንደሆነ በመግለፅ እንዲሁም የሀገር ብልፅግና ሊረጋገጥ የሚችለው በታታሪ ልጆቿ እጆች በመሆኑ ይህ ዛሬ የተሰጣችሁ እውቅና እና ሽልማት ለበለጠ ውጤት ሊያተጋችሁ ይገባል በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡



Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።