
የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁት በተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ሽኝት ተደረገላቸው፡፡
ሐምሌ 17 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
====================
የኢፌዲሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የጥራት መሰረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዲኤታ አቶ እንዳለው መኮንን እና የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) የኢትዮጵያ ተወካይ እና በአፍሪካ ህብረት የቀጠናው ዳይሬክተር ሆነው ያገለገሉትን ኦሬሊያ ፓትሪዚያ ካላብሮ አሸኛኘት አድርገውላቸዋል፡፡
በሚኒስቴር መ/ቤቱ የጥራት መሰረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እንዳለው መኮንን ኦሬሊያ ፓትሪዚያ ካላብሮ በነበራቸው የስራ ጊዜ በጥራት መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በተለይም በማር እሴት ሰንሰለት የጥራት ቁጥጥር አቅም ግንባታ ፕሮጀክትን በመደገፍ ላበረከቱት አመራርነት አመስግነው፤በራሳቸውና በጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት ስም ቀጣይ የሥራ ዘመናቸው የተቃና እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
Related Posts
ኢተምድ ለኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
የኢተምድ የሥራ ኃላፊዎች ከICIPE የሥራ ኃላፊዎች ጋር የማር ምርት ጥራት ማስጠበቅን በተመለከተ ተወያዩ ።
ኢተምድ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡