የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁት በተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ሽኝት ተደረገላቸው፡፡
ሐምሌ 17 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
====================
የኢፌዲሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የጥራት መሰረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዲኤታ አቶ እንዳለው መኮንን እና የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች የስራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) የኢትዮጵያ ተወካይ እና በአፍሪካ ህብረት የቀጠናው ዳይሬክተር ሆነው ያገለገሉትን ኦሬሊያ ፓትሪዚያ ካላብሮ አሸኛኘት አድርገውላቸዋል፡፡
በሚኒስቴር መ/ቤቱ የጥራት መሰረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እንዳለው መኮንን ኦሬሊያ ፓትሪዚያ ካላብሮ በነበራቸው የስራ ጊዜ በጥራት መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በተለይም በማር እሴት ሰንሰለት የጥራት ቁጥጥር አቅም ግንባታ ፕሮጀክትን በመደገፍ ላበረከቱት አመራርነት አመስግነው፤በራሳቸውና በጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት ስም ቀጣይ የሥራ ዘመናቸው የተቃና እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።