የኢፌዲሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር በብሔራዊ የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት እየተከናወኑ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ፡፡
ሐምሌ 02 ቀን 2016ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የብሔራዊ የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት የቢሮና የላብራቶሪ ግንባታ ፕሮጀክቶች ያሉበትን ሁኔታ በአካል በመገኘት ክትትልና ድጋፍ አደረጉ፡፡
ፕሮጀክቶቹ እንደሀገር ከፍተኛ ትኩረት የተሰጣቸው መሆናቸውን አፅንኦት በመስጠት የፕሮጀክቶቹ ቀሪ ሥራዎች በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ በመግለፅ ሁሉም በዚህ ፕሮጀክት ተሳታፊ የሆኑ አካላት ደግሞ ለፕሮጀክቶቹ በተለየ መልኩ ትኩረት ሰጥተው በፍጥነት እና በጥራት ተጠናቀው አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ክትትልና ድጋፍ ባደረጉበት ወቅት አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።