የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለሥራ መሪዎችና ሠራተኞቹ “ከእዳ ወደ ምንዳ” በሚል ርእስ እና በሌሎች ዋና ዋና አገራዊ ጉዳዮች ላይ ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡
ጥር 29 ቀን 2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ(ኢተምድ)
=========================
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት “ከእዳ ወደ ምንዳ” በሚል ርእስ እና በሌሎች በዋና ዋና አገራዊ ጉዳዮች ላይ ለሰራተኞቹ ስልጠና መስጠት ጀመረ። ለሁለት ቀናት በሚሰጠው ስልጠና ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መዓዛ አበራ የዚህ የስልጠና ዋነኛ ዓላማ ሁሉም የድርጅቱ ሰራተኞች ከእዳ ወደ ምንዳ ለመሸጋገር የሚያስችሉ ወቅታዊ ሃገራዊ አጀንዳዎች ላይ በመወያየትና በመመካከር የተሻለ ግንዛቤ በመፍጠር ሰራተኛው የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ለማስቻል ነው። መንግስት የጀመረው የለውጥ ጉዞ የኢትዮጵያዊያንን ማህበራዊ መስተጋብርና ትሥሥር በአዲስ ሀገራዊ ገዥ ትርክት ለመገንባት ፈር የቀደደ የለውጥ ጉዞ መሆኑን፣ ሀገራዊ ኢኮኖሚያችንን ከፍፁም ቀውስና ከፍተኛ የዕዳ ጫና ለመታደግ የሚያስችል ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም በመተግበር ተጨባጭ ለውጦችን ማየት የጀመርንበት ጊዜ ላይ በመድረሳችን ሪፎርሙን ውጤታማና ወደ ማይቀለበስበት ደረጃ ለማድረስ ጠንካራ ተቋምና ዘመናዊ አሰራር የሚተገብሩ ሰራተኞች ሚና ከፍተኛ መሆኑን በመግለፅ ፕሮግራሙን አስጀምረዋል።
የመጀመሪያው ቀን ስልጠና የድርጅቱ የኮርፖሬት ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር በሆኑት አቶ ጋሻው ተስፋዬ ሃብት የመፍጠር ጉዞአችን፣ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች በሚል ርእስ በመካሄድ ላይ ይገኛል።


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።