ኢተምድ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት “ወደ ዓለም አቀፍ የተመጣጠነ ምግብ ደኅንነት” /Towards Global Food and Nutrition Security›› በሚል መሪ ቃል ከጳጉሜ 1-2/2015 ዓ/ም የተዘጋጀውን የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የእንሰት ሲምፖዚየም በሚሰጠው የተስማሚነት ምዘና አገልግሎት አጋር በመሆን ሀገር በቀል ምርቶችን በጥናትና ምርምር በመታገዝ በምርምር የተገኙ ውጤቶች፣ ወደ ማኅበረሰቡ በማድረስ ለምግብ ዋስትና ወሳኝ የሆነው እንሰት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተገቢውን ትኩረት አግኝቶ ሰፊውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ እንዲያደርግ ዩኒቨርሲቲው እያደረገ ያለውን ሥራ በመደገፍ ተቋማዊ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም በዚሁ ሲምፖዚየም ላይ በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን በመሳተፍ ኢተምድ የምርትና አገልግሎቶችን ጥራት ለማስጠበቅ እየሰጣቸው የሚገኘውን የተስማሚነት ምዘና አገልግሎቶች በተመለከተ በሲምፖዚየሙ ለተሳተፉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የማስተዋወቅ ስራ ተሰርቷል፡፡



Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።