ኢተምድ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት “ወደ ዓለም አቀፍ የተመጣጠነ ምግብ ደኅንነት” /Towards Global Food and Nutrition Security›› በሚል መሪ ቃል ከጳጉሜ 1-2/2015 ዓ/ም የተዘጋጀውን የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የእንሰት ሲምፖዚየም በሚሰጠው የተስማሚነት ምዘና አገልግሎት አጋር በመሆን ሀገር በቀል ምርቶችን በጥናትና ምርምር በመታገዝ በምርምር የተገኙ ውጤቶች፣ ወደ ማኅበረሰቡ በማድረስ ለምግብ ዋስትና ወሳኝ የሆነው እንሰት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተገቢውን ትኩረት አግኝቶ ሰፊውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ እንዲያደርግ ዩኒቨርሲቲው እያደረገ ያለውን ሥራ በመደገፍ ተቋማዊ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም በዚሁ ሲምፖዚየም ላይ በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን በመሳተፍ ኢተምድ የምርትና አገልግሎቶችን ጥራት ለማስጠበቅ እየሰጣቸው የሚገኘውን የተስማሚነት ምዘና አገልግሎቶች በተመለከተ በሲምፖዚየሙ ለተሳተፉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የማስተዋወቅ ስራ ተሰርቷል፡፡



Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።