
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት (ኢተምድ) የሥራ አመራር አባላት እና ሰራተኞች ከንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ከሌሎች ለሚኒስቴር መ/ቤቱ ተጠሪ ከሆኑ ተቋማት ጋር በጋራ በመሆን ሐምሌ 25ቀን 2015ዓ.ም በሰበታ ሀዋስ ወረዳ ደበል ተራራ ላይ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሂደዋል፡፡
በችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ ላይ የድርጅቱ የበላይ አመራሮች እንደሀገር የተያዘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ችግኝ መትከል ለትውልድ የሚተላለፍ ቅርስ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባ ተግባር እንደሆነ እና ለተተከለው ችግኝም ተገቢውን እንክብካቤ ማድረግ ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ስራ መሆኑን መልእክት አስተላልፈዋል።
Related Posts
ኢተምድ ለኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
የኢተምድ የሥራ ኃላፊዎች ከICIPE የሥራ ኃላፊዎች ጋር የማር ምርት ጥራት ማስጠበቅን በተመለከተ ተወያዩ ።
ኢተምድ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡