የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት (ኢተምድ) የሥራ አመራር አባላት እና ሰራተኞች ከንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ከሌሎች ለሚኒስቴር መ/ቤቱ ተጠሪ ከሆኑ ተቋማት ጋር በጋራ በመሆን ሐምሌ 25ቀን 2015ዓ.ም በሰበታ ሀዋስ ወረዳ ደበል ተራራ ላይ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሂደዋል፡፡
በችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ ላይ የድርጅቱ የበላይ አመራሮች እንደሀገር የተያዘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ችግኝ መትከል ለትውልድ የሚተላለፍ ቅርስ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባ ተግባር እንደሆነ እና ለተተከለው ችግኝም ተገቢውን እንክብካቤ ማድረግ ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ስራ መሆኑን መልእክት አስተላልፈዋል።


Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።