
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሥራ አመራር አባላት እና ሰራተኞች ከንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር መ/ቤትና ከሌሎች ተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ሐምሌ 10ቀን 2015ዓ.ም “ነገን ዛሬ እንትከል” በሚል መሪ ቃል የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በቂሊንጦ ኢንዱስትሪያል ፓርክ አካሂደዋል፡፡ በዛሬው እለት በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል በተደረገው አገራዊ ንቅናቄ መርሃ-ግብር ላይ የኢተምድ የሥራ አመራር አባላት እና ሰራተኞች የራሳቸውን ታሪካዊ አሻራ አስቀምጠዋል።
Related Posts
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አመራርና ሠራተኞች ኢተምድን ጎበኙ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢተምድ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡