ኢተምድ በአዳማ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ፡፡

የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሚሰጣቸውን የጥራት ፍተሻ ላብራቶር፣ የኢንስፔክሽንና የሰርቲፊኬሽን አገልግሎቶችን ለማስተዋወቅ እና የአገልግሎቶቹን ተደራሽነት ለማስፋት እያከናወናቸው የሚገኙ የአቅም ግንባታ ተግባራትን እንዲሁም በምግብ ዘርፍ ጥራትን ከማስጠበቅ አንፃር እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን በሚመለከት ከFood Enterprise Solutions ጋር በመተባበር በዘርፉ ለተሰማሩ አምራቾች፣ አገልግሎት ሰጪዎች፣አስመጪዎችና ላኪዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ሰኔ 27ቀን 2015ዓ.ም በአዳማ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ፡፡