የኢ.ፌ.ዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን የስራ ኃላፊዎች የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የፍተሻ ላቦራቶሪዎችን ጎበኙ፡፡ የጉብኝቱ ዓላማ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የምርቶችንና አገልግሎቶች ጥራትን ከማስጠበቅ አንፃር ያለውን አገልግሎት የመስጠት አቅም በአካል ተገኝተው በመጎብኘት በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ነበር፡፡
በጉብኝቱም በግዥ ሂደት ውስጥ የሚካተቱ ምርቶች በተስማሚነት ምዘና ሂደት ውስጥ የሚያልፉበትና የጥራት ቁጥጥር የሚደረግበትን አግባብ በመዘርጋት የተሻለ ጥራት ያለው ምርት በመግዛትና በማቅረብ የግዥ አፈፃፀም ሥርዓቱን የበለጠ ሀብትና ጊዜ ቆጣቢ እንዲሁም በውድድር ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ለማስቻል በቅንጅት በመስራት አገራዊ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን ለማስገኘት በሚያችሉ ሁኔታዎች ላይ ከኢተምድ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡


Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።