
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ክትትልና ድጋፍ ከሚያደርግባቸው የፌደራል መ/ቤቶች አንዱ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ሲሆን የኢተምድን ተግባራትና አሰራር፣የሚሰጣቸውን የጥራት ፍተሻ ላብራቶር፣የኢንስፔክሽንና የሰርቲፊኬሽን አገልግሎቶች እና ተደራሽነቱን ለማስፋት እያከናወናቸው በሚገኙ የአቅም ግንባታ ተግባራት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ሰኔ 17 ቀን 2015ዓ.ም በአዳማ ከተማ ሰጥቷል፡፡ የግንዛቤ ማስጨበጫው በድርጅቱ ተግባራትና አሰራር ላይ ግልፅነት በመፍጠር የቋሚ ኮሚቴውን የክትትልና ድጋፍ ስራ ውጤታማ ለማድረግ ያለመ ነበር፡፡
Related Posts
ኢተምድ ለኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
የኢተምድ የሥራ ኃላፊዎች ከICIPE የሥራ ኃላፊዎች ጋር የማር ምርት ጥራት ማስጠበቅን በተመለከተ ተወያዩ ።
ኢተምድ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡