
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ክትትልና ድጋፍ ከሚያደርግባቸው የፌደራል መ/ቤቶች አንዱ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ሲሆን የኢተምድን ተግባራትና አሰራር፣የሚሰጣቸውን የጥራት ፍተሻ ላብራቶር፣የኢንስፔክሽንና የሰርቲፊኬሽን አገልግሎቶች እና ተደራሽነቱን ለማስፋት እያከናወናቸው በሚገኙ የአቅም ግንባታ ተግባራት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ሰኔ 17 ቀን 2015ዓ.ም በአዳማ ከተማ ሰጥቷል፡፡ የግንዛቤ ማስጨበጫው በድርጅቱ ተግባራትና አሰራር ላይ ግልፅነት በመፍጠር የቋሚ ኮሚቴውን የክትትልና ድጋፍ ስራ ውጤታማ ለማድረግ ያለመ ነበር፡፡
Related Posts
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አመራርና ሠራተኞች ኢተምድን ጎበኙ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢተምድ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡