የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታዎች ክብርት ሁሪያ አሊ፣ክቡር ዶ/ር ባይሳ በዳዳ፣ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ተመራማሪዎች በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት/ኢተምድ/ በመገኘት የሥራ ጉብኝት አደረጉ።
በጉብኝቱ በኢተምድ የሚገኙትን የፍተሻ ላብራቶሪዎች፣የሚሠጡት የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች እና የአቅም ግንባታ ሥራዎች በአካል በመገኘት የጎበኙ ሲሆን በቀጣይ ኢተምድ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመን እና በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር በጋራ ተቀናጅቶ ለመስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።