የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታዎች ክብርት ሁሪያ አሊ፣ክቡር ዶ/ር ባይሳ በዳዳ፣ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ተመራማሪዎች በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት/ኢተምድ/ በመገኘት የሥራ ጉብኝት አደረጉ።
በጉብኝቱ በኢተምድ የሚገኙትን የፍተሻ ላብራቶሪዎች፣የሚሠጡት የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች እና የአቅም ግንባታ ሥራዎች በአካል በመገኘት የጎበኙ ሲሆን በቀጣይ ኢተምድ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመን እና በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር በጋራ ተቀናጅቶ ለመስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።