የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታዎች ክብርት ሁሪያ አሊ፣ክቡር ዶ/ር ባይሳ በዳዳ፣ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ተመራማሪዎች በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት/ኢተምድ/ በመገኘት የሥራ ጉብኝት አደረጉ።
በጉብኝቱ በኢተምድ የሚገኙትን የፍተሻ ላብራቶሪዎች፣የሚሠጡት የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች እና የአቅም ግንባታ ሥራዎች በአካል በመገኘት የጎበኙ ሲሆን በቀጣይ ኢተምድ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመን እና በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር በጋራ ተቀናጅቶ ለመስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

Related Posts
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢተምድ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤትን የሥራ እንቅስቃሴ ጎበኙ፡፡
የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሥራ እንቅስቃሴ ገመገሙ፡፡
ኢተምድ በአዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)