
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታዎች ክብርት ሁሪያ አሊ፣ክቡር ዶ/ር ባይሳ በዳዳ፣ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ተመራማሪዎች በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት/ኢተምድ/ በመገኘት የሥራ ጉብኝት አደረጉ።
በጉብኝቱ በኢተምድ የሚገኙትን የፍተሻ ላብራቶሪዎች፣የሚሠጡት የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች እና የአቅም ግንባታ ሥራዎች በአካል በመገኘት የጎበኙ ሲሆን በቀጣይ ኢተምድ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመን እና በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር በጋራ ተቀናጅቶ ለመስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡
Related Posts
ኢተምድ ለኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
የኢተምድ የሥራ ኃላፊዎች ከICIPE የሥራ ኃላፊዎች ጋር የማር ምርት ጥራት ማስጠበቅን በተመለከተ ተወያዩ ።
ኢተምድ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡