በገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት/ኢተምድ/ በመገኘት የሥራ ጉብኝት አደረጉ።
የጉብኝቱ አላማም በድርጅቱ የሚሠጡት የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች እና በዓለም ባንክ ፕሮጀክት እየተሰሩ ያሉትን የአቅም ግንባታ ሥራዎች በአካል በመገኘት ያሉበትን ደረጃ መጎብኘት እና በቀጣይ ድርጅቱ የሚሰጠውን አገልግሎት በተሻለ ሁኔታ እንዲያከናውን ከተለያዩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ጋር በመቀናጀት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እና ተመራጭ ተቋም እንዲሆን ያለመ ነበር፡፡

Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።