
127ኛው የዓድዋ ድል በዓልን “የዓድዋ ድል በዓል ለአገራዊ አንድነት፣ጀግንነት እና ጽናት መህልቅ” በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት እና የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት የሥራ አመራር አባላት እና ሰራተኞች በጋራ አከበሩ፡፡
በዓሉን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ የከፈቱት የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሠረት በቀለ ዓድዋ የነፃነት ቀን ሳይሆን የድል ቀን በመሆኑ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ሊኮራበት የሚገባ መሆኑና ዓድዋ ያለ አንዳች ልዩነት ኢትዮጵያዊያን የጋራ መስዋዕትነት ተከፍለውበት የተገኘ ድል በመሆኑ ከሀገር ኩራትነት ባሻገር በዓለም ለሚገኙ ጥቁር ህዝቦች በሙሉ የኩራት ምልክት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በበዓሉ ላይ የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር ቀኑን በማስመልከት ያዘጋጀው አጭር የመወያያ ፅሁፍ ቀርቦ ከተሳታፊ ሰራተኞች አስተያየትና ጥያቄዎች ቀርበው ውይይት ተካሂዷል፡፡ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መአዛ አበራ በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልእክት ከዓድዋ ድል የወሰድነውን የጀግንነት መንፈስ በወቅታዊው ሀገራዊ ሁኔታ ላይ ልንጠቀምበት እንደሚገባ ገልፀው የአሁኑ ትውልድ ሀገራችን ካለችበት የድህነት ታሪክ የማሻገር ድርሻውን ለመወጣት በዓድዋ ጀግኖቻችን የትብብርና የአንድነት መንፈስ ሁሉም የዜግነት ድርሻውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡


Related Posts
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አመራርና ሠራተኞች ኢተምድን ጎበኙ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢተምድ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡