የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ከዓለም አቀፍ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ጋር በትብብር ያስገነባው የፀሐይ ኃይል ምርቶች መፈተሻ ላቦራቶሪ ሥራ ጀመረ። ላቦራቶሪው እስከ 350 ዋት የሚደርሱ የፀሐይ ኃይል ምርቶችን ለመፈተሽ የሚያስችል አቅም አለው።
የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መዓዛ አበራ በላብራቶሪው ምርቃት ስነ-ስርዓት ወቅት እንደገለጹት ከውጭ የሚገቡና በሀገር ውስጥ የሚመረቱ በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ ምርቶችን ጥራት ለማረጋገጥ በኢተምድ በርካታ ሥራዎች ሲሠሩ ቆይተዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ተቋማት ድጋፍ ዘመናዊ በፀሐይ ኃይል የሚሰሩ ምርቶች መፈተሻ ላቦራቶሪ ተገንብቶ ወደ ሥራ መግባቱን ጠቁመዋል። ላብራቶሪው ለገጠር ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚውሉ የፀሐይ ኃይል ምርቶችን በመፈተሽና የምስክር ወረቀት በመስጠት እንዲሁም ከተቆጣጣሪ መ/ቤቶች ጋር በመስራት ጥራት የሌላቸውን ምርቶች ከገበያ ውጭ በማድረግ የተጠቃሚውን ህብረተሰብ ደህንነት ለመጠበቅ እንደሚያስችልም ገልጸዋል፡፡ ከውጪ የሚገቡ ምርቶች ኢትዮጵያ ያወጣቺውን አስገዳጅ መስፈርቶች ማሟላታቸውን የቅድመ ጭነት ፍተሻ በማድረግ በሚያገኙት ማረጋገጫ ምርቶቹ እንደሚገቡም ተገልጿል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።