ኢተምድ ከFITI Testing & Research Institute ጋር በመተባበር ለቆዳና ጨርቃጨርቅ ፍተሻ ባለሙያዎች ስልጠና እየሠጠ ይገኛል፡፡
ከኮሪያው የፍተሻ ላቦራቶርና የምርምር ኢንስቲትዩት (FITI Testing & Research Institute) ጋር በመተባበር ለኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የቆዳና ጨርቃ ጨርቅ ፍተሻ ባለሙያዎች በ5 የተለያዩ የፍተሻ ባህሪያት ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡
የአቅም ግንባታ ስልጠናው በቆዳና ጨርቃ ጨርቅ ፍተሻ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተቀባይነትና እውቅናን በጠበቀ መልኩ ድርጅቱ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን በስራ ላይ ስልጠና፣ የልምድ ልውውጥ፣ ቴክኒካል ሙያዊ ድጋፍ፣ የፍተሻ ዘዴዎችን ማበልፀግ፣ በሌሎች ሀገራት በሚደረጉ የፍተሻ ንፅፅር ላይ ባለሙያዎች እንዲሳተፉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንዲሁም በቆዳና ጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ የሰርቲፊኬሽን ወሰኖችን ለማስፋት የሚያስችሉ ቴክኒካል ድጋፎ ችን ያጠቃልላል፡፡




Related Posts
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አዳማ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ እና የፍተሻ ላብራቶሪ በይፋ አስመረቀ። ጥር 16/2018 ዓ/ም አዳማ (ኢተምድ)
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።