
ኢተምድ ከFITI Testing & Research Institute ጋር በመተባበር ለቆዳና ጨርቃጨርቅ ፍተሻ ባለሙያዎች ስልጠና እየሠጠ ይገኛል፡፡
ከኮሪያው የፍተሻ ላቦራቶርና የምርምር ኢንስቲትዩት (FITI Testing & Research Institute) ጋር በመተባበር ለኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የቆዳና ጨርቃ ጨርቅ ፍተሻ ባለሙያዎች በ5 የተለያዩ የፍተሻ ባህሪያት ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡
የአቅም ግንባታ ስልጠናው በቆዳና ጨርቃ ጨርቅ ፍተሻ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተቀባይነትና እውቅናን በጠበቀ መልኩ ድርጅቱ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን በስራ ላይ ስልጠና፣ የልምድ ልውውጥ፣ ቴክኒካል ሙያዊ ድጋፍ፣ የፍተሻ ዘዴዎችን ማበልፀግ፣ በሌሎች ሀገራት በሚደረጉ የፍተሻ ንፅፅር ላይ ባለሙያዎች እንዲሳተፉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት እንዲሁም በቆዳና ጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ የሰርቲፊኬሽን ወሰኖችን ለማስፋት የሚያስችሉ ቴክኒካል ድጋፎ ችን ያጠቃልላል፡፡
Related Posts
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አመራርና ሠራተኞች ኢተምድን ጎበኙ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢተምድ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡