የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት ጋር በጋራ የዓለም የጥራት ቀንን አስመልክቶ ያዘጋጁት ኤግዚቢሽን ተከፈተ። ኤግዚቢሽኑን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ ገብረ መስቀል ጫላ ከሌሎች የዘርፉ ሚ/ዲኤታዎች እና የተቋማቱ ዋና ዳይሬክተሮች ጋር በጋራ ከፍተውታል። “በጥራት የተቃኘ ህሊና ትክክለኛ ተግባርን ለመከወን” በሚል መሪ ቃል የተከፈተው ይህ ኤግዚቢሽን ከህዳር 15-17/2015ዓ.ም ለሶስት ቀናት የሚቆይ ሲሆን ከአራቱም የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት ጋር በጥራት ዙሪያ የሚሰሩ የምርት ጥራት ማረጋገጫ ያገኙ ድርጅቶች ተሳትፈውበታል፡፡ ኤግዚቢሽኑ ለሶስት ቀናት ለህዝብ ክፍት የሚሆን ሲሆን ህብረተሰቡ በኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ቅጥር ግቢ በመገኘት ይህንን ኤግዚቢሽን እንዲጎበኝ ተጋብዟል፡፡



Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።