
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት ጋር በጋራ የዓለም የጥራት ቀንን አስመልክቶ ያዘጋጁት ኤግዚቢሽን ተከፈተ። ኤግዚቢሽኑን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ ገብረ መስቀል ጫላ ከሌሎች የዘርፉ ሚ/ዲኤታዎች እና የተቋማቱ ዋና ዳይሬክተሮች ጋር በጋራ ከፍተውታል። “በጥራት የተቃኘ ህሊና ትክክለኛ ተግባርን ለመከወን” በሚል መሪ ቃል የተከፈተው ይህ ኤግዚቢሽን ከህዳር 15-17/2015ዓ.ም ለሶስት ቀናት የሚቆይ ሲሆን ከአራቱም የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት ጋር በጥራት ዙሪያ የሚሰሩ የምርት ጥራት ማረጋገጫ ያገኙ ድርጅቶች ተሳትፈውበታል፡፡ ኤግዚቢሽኑ ለሶስት ቀናት ለህዝብ ክፍት የሚሆን ሲሆን ህብረተሰቡ በኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት ቅጥር ግቢ በመገኘት ይህንን ኤግዚቢሽን እንዲጎበኝ ተጋብዟል፡፡
Related Posts
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን አመራርና ሠራተኞች ኢተምድን ጎበኙ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡
የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢተምድ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡