
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለዴይላይት አፕላይድ ቴክኖሎጂስ ኃ.የተ.የግ.ማ በምግብ ደህንነት ስራ አመራር ስርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ፡፡
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በምግብ ደህንነት ስራ አመራር ስርዓት ISO: 22000:2018 ደረጃ መስፈርትን በማሟላታቸው የምግብ ማሸጊያ የቆርቆሮ ጣሳ በማምረት (producing, packing and storing of tin can for food packaging) ለዴይላይት አፕላይድ ቴክኖሎጂስ ኃ.የተ.የግ.ማ ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡ የዴይላይት አፕላይድ ቴክኖሎጂስ ኃ.የተ.የግ.ማ ተወካይ የሆኑት ወ/ሮ መአዛ መርሻ በምግብ ደህንነት ስራ አመራር ስርዓት ሰርተፊኬት ለማግኘት ኢተምድ ላደረገላቸው ሙያዊ የኦዲት ስራዎችና ለተሰጣቸው ሰርተፍኬት አመስግነው፤በቀጣይም ጥራትን ለማስጠበቅ በጋራ መስራት የድርጅታቸው ፍላጎት መሆኑን ሰርተፍኬቱን ከኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መአዛ አበራ በተቀበሉበት ጊዜ ገልፀዋል፡፡
Related Posts
3ኛው የአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት ጉባኤ ተሳታፊዎች የኢተምድ ላቦራቶሪዎችን ጎበኙ።
የኢተምድ አመራርና ሠራተኞች በ2018 ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡
የኢተምድ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ የችግኝ ተከላ መርሃግብር አካሄዱ።