የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለዴይላይት አፕላይድ ቴክኖሎጂስ ኃ.የተ.የግ.ማ በምግብ ደህንነት ስራ አመራር ስርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ፡፡
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በምግብ ደህንነት ስራ አመራር ስርዓት ISO: 22000:2018 ደረጃ መስፈርትን በማሟላታቸው የምግብ ማሸጊያ የቆርቆሮ ጣሳ በማምረት (producing, packing and storing of tin can for food packaging) ለዴይላይት አፕላይድ ቴክኖሎጂስ ኃ.የተ.የግ.ማ ሰርተፍኬት ሰጠ፡፡ የዴይላይት አፕላይድ ቴክኖሎጂስ ኃ.የተ.የግ.ማ ተወካይ የሆኑት ወ/ሮ መአዛ መርሻ በምግብ ደህንነት ስራ አመራር ስርዓት ሰርተፊኬት ለማግኘት ኢተምድ ላደረገላቸው ሙያዊ የኦዲት ስራዎችና ለተሰጣቸው ሰርተፍኬት አመስግነው፤በቀጣይም ጥራትን ለማስጠበቅ በጋራ መስራት የድርጅታቸው ፍላጎት መሆኑን ሰርተፍኬቱን ከኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መአዛ አበራ በተቀበሉበት ጊዜ ገልፀዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።