የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎች ኢተምድን ጎበኙ፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል የተመሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት (ኢተምድ) የስራ ጉብኝት አካሂደዋል፡፡ የጉብኝቱ ዓላማ የምርቶችንና አገልግሎቶች ጥራትን ከማስጠበቅ አንፃር የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተልእኮዎችን ከማስፈጸም አንፃር ያለውን አቅም በአካል ተገኝተው በመጎብኘት በጋራ ለመስራት የሚያስችል ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ያለመ ነበር፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የኢተምድ ዘጠኝ የፍተሻ ላብራቶሮች፣ የኢንስፔክሽንና የሰርቲፊኬሽን የአሰራር ስርዓቶች እና አገልግሎት የመስጠት አቅሙ በኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መአዛ አበራ እና በኦፕሬሽን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አቤል አንበርብር ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ከጉብኝቱ በኃላ ኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቃቱን በማረጋገጥ የምርቶችና አገልግሎቶች የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት የመስጠት አቅሙ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንድትሆን የሚያስችል ቁመና ያለው ድርጅት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በመጨረሻም ሚኒስቴር መ/ቤቱና ኢተምድ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ጉብኝት ማድረጋቸውን አረጋግጠዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።