
ወ/ሮ መአዛ አበራ ከጷጉሜ 4/2014 ዓ/ም ጀምሮ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት (ኢተምድ) ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተርዋ የድርጅቱ ላቦራቶሮችን በመጎብኘትና ከስራ አመራር አባላት ጋር በመተዋወቅ ስራቸውን የጀመሩ ሲሆን በወቅቱ የድርጅቱን ቀጣይ ስራዎች አቅጣጫ በማስቀመጥ ስኬታማ የስራ ዘመን እንዲሆን ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡
የኢተምድ የስራ አመራር አባላትና ሰራተኞችም መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው ልባዊ ምኞታችንን እንገልፃለን፡፡

Related Posts
ኢተምድ ለኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
የኢተምድ የሥራ ኃላፊዎች ከICIPE የሥራ ኃላፊዎች ጋር የማር ምርት ጥራት ማስጠበቅን በተመለከተ ተወያዩ ።
ኢተምድ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡