ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢግልድ) ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች የተውጣጡ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች በኢተምድ የስራ ጉብኝት አካሂደዋል፡፡ የጉብኝቱ ዓላማ በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የምርቶች የጥራት ፍተሻ ሂደትን በአካል ተገኝተው መጎብኘት፣ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችንና ምርቶችን ጥራትን ከማስጠበቅ አንፃር ሁለቱ ድርጅቶች በቀጣይ በጋራ የሚሰሩበትን ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እና እንደ ልማት ድርጅትነታቸው የልምድ ተሞክሮ ልውውጥ ማድረግን ታሳቢ ያደረገ ነበር፡፡ በጉብኝቱ የኢተምድ ላብራቶር ፍተሻ፣ የኢንስፔክሽን፣የሰርቲፊኬሽን አገልግሎቶች አሰጣጥ እና ኢተምድ አዘጋጅቶ ተግባራዊ እያደረገው ባለው የኮርፖሬት ማህበራዊ ሓላፊነት መመሪያን (Corporate Social Responsibility Guideline) በተመለከተ በድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተሻለ በልሁ አማካኝነት ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡ በእለቱ በድርጅቱ ውስጥ የጥራት ፍተሻ የሚከናወንባቸውን 9 ላብራቶሪዎች በመዘዋወር ጎብኝተዋል፡፡
ኢግልድ በብቁ የሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ በተደገፈ የአሰራር ስርዓት በመታገዝ እና ጠንካራ የአቅርቦትና ግብይት ሰንሰለት በመፍጠር ጥራታቸውን የጠበቁ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን በማልማት፣በማቅረብ እና የተመረጡ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች ተደራሽ በማድረግ የሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አስተዋጽኦ ማድረግና ገበያ ማረጋጋትን ተልእኮው በማድረግ የሚሰራ ድርጅት በመሆኑ ይህን ተልእኮውን በብቃት ለመከወን ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የፍተሻ ላቦራቶር፣የኢንስፔክሽንና ሰርቲፊኬሽን የአሰራር ሥርዓቶችን በመተግበር ተዓማኒነት ያለው፣ገለልተኛ፣ውጤታማ፣ተደራሽና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ጥራት ያለው ምርትና አገልግሎት እንዲኖር ከሚሰራው የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ኃላፊዎቹ ገልፀዋል፡፡

Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።