ሰኔ 30 ቀን 2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለቀጠራቸው አዲስ ሰራተኞች የትውውቅ መርሐ-ግብር አከናውኗል፡፡ መርሐ-ግብሩ አዲሶቹን ሰራተኞችን ከድርጅቱ ጋር ለማዋሃድ የኢተምድን የአሰራር ስርአቶች፣የድርጅቱን ባህል፣ እሴቶችን እና ድርጅቱን በተመለከተ ሌሎች ጠቃሚ መረጃዎችን በመስጠት ግንዛቤ መፍጠርን አላማው ያደረገ ነው። እንዲሁም አዲስ ሰራተኞች ወደ አዲስ የስራ አካባቢ በሚቀላቀሉበት ጊዜ የሚፈጠር የእንግድነት ስሜትን ለማስቀረት እና ከነባር ሰራተኞች ጋር ለማስተዋወቅ ያለመ ነው፡፡
በትውውቅ መርሐ-ግብሩ ላይ የኢተምድን ገፅታ፣ የዋና የስራ ሂደቶች አሰራር፣ የሰው ሃብት መመሪያዎች እና የሰራተኛ መብትና ግዴታ በተመለከተ ገለፃ የቀረበላቸው ሲሆን አዲስ ተቀጣሪ ሰራተኞችም ግልፅ እንዲሆንላቸው የሚፈልጉትን ጥያቄዎች በማንሳት ምላሽ ከሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች ተሰጥቷቸዋል፡፡ በመርሐ-ግብሩ መጨረሻ የድርጅቱን የፍተሻ ላብቶሪዎችም ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን አዲስ ተቀጣሪ ሰራተኞችም ስለተደረገላቸው አቀባበልና ገለፃ በማመስገን የድርጅቱን ስራዎች ለማወቅ እንዳስቻላቸው እና በሌሎች ድርጅቶችም ቢለመድ ጥሩ ተሞክሮ እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡


Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።