የአዲሱ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር በሆኑት አቶ ገብረመስቀል ጫላ የተመራ የሚኒስቴር መ/ቤቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ከኢተምድ እና ከሶስቱ የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት የሥራ አመራር አባላት ጋር በመሆን የተቋማቶቹን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝታቸውም የአራቱ የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት የአሰራር ስርዓት እና አገልግሎት በተመለከተ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡
የሥራ ኃላፊዎቹ የኢተምድን ላብራቶሮች ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ድርጅቱ ካለው እና እየገነባ ከሚገኘው አቅም አንፃር በርካታ ስራዎች እየሰራ የሚገኝ ተቋም መሆኑን ገልፀው ለወደፊትም በርካታ ሥራዎች መስራት የሚጠበቅበት የሀገራቱ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ሊሆን የሚገባው ተቋም እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር የሆኑት ክቡር አቶ ገ/መስቀል ጫላ በቀጣይ በዘርፉ ያሉ የስራ አፈፃፀሞችን ለማሻሻል የሚያስችል የ100 ቀናት እቅድ በማዘጋጀት ትኩረት ተደርጎ ሊሰሩ የሚገቡ ስራዎችን ለይቶ በማቀድ እንዲሰሩ የስራ መመሪያ በመስጠት ተቋማቶቹ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ የሚፈልጉት ድጋፎች እንደማይለያቸው በማረጋገጥ የሥራ ጉብኝታቸውን አጠናቀዋል፡፡








Related Posts
የኢተምድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን አከበረ፡፡ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)
“ጥራት፡ በተለየ እሳቤና ፈጠራ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የጥራት ሳምንት በጥራት መንደር ውስጥ የተዘጋጀውን የጥራት ኤክስፖ ተጠናቀቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተገኙበት አምስት ተቋማትን በአንድ ላይ በመያዝ የተደራጀው የጥራት መንደር አንደኛ ዓመት በዛሬው ዕለት በደማቅ መረሃ ግብር ተከብሯል ።