
ኢተምድ የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት እቅድ አፈፃፀሙን ገመገመ፡፡
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በ2013 በጀት ዓመት የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት 9‚299 የአገልግሎት ጥያቄዎችን በማስተናገድ የምርት ጥራት የላብራቶር ፍተሻ፣ የወጪና ገቢ ምርት ኢንስፔክሽን እና የሰርተፍኬሽን አገልግሎቶችን በመስጠት ጥራት ያለው ምርትና አገልግሎት እንዲኖር እና ፍትሃዊ የግብይት ስርዓት እንዲሰፍን ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል፡፡እነዚህም አገልግሎቶች ለ6‚853 የምርት ናሙናዎች የላብራቶር ፍተሻ አገልግሎት፣ ለ2‚110 ገቢ እና ወጪ የምርት ናሙናዎች እና 10 መርከብ የስንዴና የአፈር ማዳበሪያ ጭነት የኢንስፔክሽን አገልግሎት እና ለ326 የሰርተፍኬሽን አገልግሎቶች ይገኙበታል፡፡
Related Posts
3ኛው የአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት ጉባኤ ተሳታፊዎች የኢተምድ ላቦራቶሪዎችን ጎበኙ።
የኢተምድ አመራርና ሠራተኞች በ2018 ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡
የኢተምድ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ የችግኝ ተከላ መርሃግብር አካሄዱ።