ኢተምድ የሚለው ምህፃረ ቃል ፡ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት” ይወክላል፡፡ ኢተምድ በጥር ወር 2003ዓ.ም በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 196/2003 በፌደራል ደረጃ የመንግስት የልማት ድርጅት ሆኖ የተስማሚነት ምዘና አገልግሎቶችን ለመስጠት ተቋቁሟል፡፡ የድርጅቱ ተቆጣጣሪ ባለስልጣን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ነው፡፡
ኢተምድ በዋነኝነት የተስማሚነት ምዘና አገልግሎቶች ማለትም የላብራቶር ፍተሻ፣የኢንስፔክሽንና የሰርቲፊኬሽን አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን በስሩ ከ200 በላይ ሰራተኞችን ይዞ 8 ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን በመላው ሀገሪቱ በማደራጀት እየሰራ የሚገኝ ድርጅት ነው፡፡
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የፍተሻ ላቦራቶር፣የኢንስፔክሽንና ሰርቲፊኬሽን የአሰራር ሥርዓቶችን በመተግበር ተዓማኒነት ያለው፣ገለልተኛ፣ውጤታማ፣ተደራሽና ቀልጣፋ የተስማሚነት ምዘና አገልግሎት በመስጠት ጥራት ያለው ምርትና አገልግሎት እንዲኖር ማስቻልን ዓላማው አድርጎ የሚሰራ ድርጅት ነው፡፡
Related Posts
3ኛው የአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት ጉባኤ ተሳታፊዎች የኢተምድ ላቦራቶሪዎችን ጎበኙ።
የኢተምድ አመራርና ሠራተኞች በ2018 ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡
የኢተምድ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ የችግኝ ተከላ መርሃግብር አካሄዱ።